የእሴይ መሰረታዊ የቁጠባና ብድር ህብረት ስራ ማህበር አጭር መዋቅርና ታሪክ እሴይ መሰረታዊ የቁጠባና ብድር ህብረት ስራ ማህበር ሊቀየር የማይችለውን የጋራ አላማና ራዕይ ያነገቡ፣ እርስ በርስ ለመደጋገፍና በጋራ ለማደግ የቆረጡ 222 መስራች አባላትን በማስተባበር በጥቅምት 10 ቀን 2017 ዓ.ም. (October 20, 2024) ተመሠረተ። ማህበሩ በህግ የታወቀና ህጋዊ ሰውነት ያገኘ ተቋም ሲሆን፣ በታወጀው የአዋጅ ቁጥር 985/2009 (Proclamation No. 985/2017) መሠረት ተደራጅቷል። በዚሁ መሰረት በህዳር 16 ቀን 2017 ዓ.ም. (November 25, 2024) ከኢትዮጵያ ህብረት ስራ ኮሚሽን በምዝገባ ቁጥር ECC/008/17 ህጋዊ የስራ ፍቃድ አግኝቶ ይፋዊ ስራውን ጀምሯል።